የደበበ እሸቱ መጽሀፍ ከቀስተ ደመና እስከ ወህኒ

ኢትዮጵያ ዛሬ በምድረ አሜሪካ የወ/ሪት ብርቱካንን አንጃ ወክሎ ለ<ደፋር ተሳዳቢነት> በዘመቻ መልክ የተላከ የሚመስለው ተውኔተኛው ደበበ እሸቱ ከ<ቀስተ ዳመና እስከ እስር ቤት> በሚል ርዕስ መጽሀፍ ለማሳተም የገንዘብ እርዳታ እየተማጸነ መሆኑ ተደረሰበት። ገፁ በዛ ያለው የ<ቲያትረኛው> ደበበ መፅሀፍ <እኔ> በሚል ስንክሳር የተጨናነቀ መሆኑን ምንጮቻችን ደርሰውበታል።
ጊዜያዊውን የአሜሪካ መኖሪያ ዋሽንግተን አካባቢ ከአርቲስት ዓለም ፀሀይ ወዳጆ ቤት ያደረገው ደበበ እሸቱ፤ ኢንጂነር ሀይሉ ሻወል ስብሰባ ሊያካሂዱ ባቀዱብት የአሜረካ ክፍለ ከተሞች ሁሉ እየተጉዋዘ ቀድሞ የስብሰባ ጥሪ በማስደረግ የሊቀ መንበሩ ስብሰባ እንዲከሽፍ ለማድረግ ሲሞክር ሰንብቱዋል። ተውኔተኛው ደበበ በደረሰባቸው ቦታዎች በጸያፍ አነጋገሩ የተነሳ ደጋፊዎቹን ሳይቀር እያሳፈረ መምጣቱን ለመረዳትም ችለናል። ደበበን በቅርብ የሚያውቁትና መዋሸት ሁለተኛ ተፈጥሮው ነው የሚሉ፤ በቀስተ ደመና ውስጥ የነበረው ተሳትፎ እጅግም እንደሆነ አበክረው ሲገልጡ፤ የሌሎችንም ታሪክ ለመቀማት ወደ ሁዋላ የሚል ተፈጥሮ እንደሌለው ይናገራሉ። መፅሀፉም ይህንኑ የሚያረጋግጥ እንደሚሆን ይገመታል።